Saturday, November 4, 2017

መደማመጥ ቢኖር ኖሮ ፦፦

https://www.youtube.com/watch?v=kb0nAeufC3o
መከባበር ላይ የተመሰረተው የመኖር ዜይቤያችን መሰረቱን ለመናድ ተወጥኖ በተደራጀ መንግስታዊ ፖልሲ አንድንማር አንድናድግ ስንደረግ መርጠን ሳይሆን ተገደን ነበር ። ይህንን ፈር  ያጣ አፍራሽነት ማስተዋል የቻሉ የገዥዎች እጀ ሰፊነት ሳያስፈራቸው መከባበራችንን አንድነታችንን መልሱልን በቃችሁ ማለት መቻላቸውን ከእለት ወደ እለት በሀገሬ ማየት መቻሌ ነገሮችን ሰከን ብዬ ማስተዋል እና የተውለድኩበትን የተማርኩበትን ስርአተትምህርት አና ስርአት ከማማረር ይልቅ ፍትሕ  መከባበር እና በሁሉ የሁሉ የሆነ ስርአት መስራት እችላለሁ የምል እንድሆን አድርጎኛል ። 

በእርግጥ መከባበራችንን የሚያስተምሩን ለእኔ እና አንተ የሆነችውን ሀገር ለመስራት አለኝ የሚሉት ሃብት ንብረት እንዲሁም ህይወታቸውን እየገበሩ ያሉ ወገኖች ወገን ስማ ብለው ሲጮሁ ያለመስማታችን ፈተናችንን አበዛብን ። 
በተለይ ወጣቱ ትውልድ የኔ የምትለውን እየቀሙህ ያሉት ጠባቦች አንተን መስለው ሲገሉህ የማይሽንጥህ ምን ሆነህ ነው ??? 
 ወገን መደማመጥ ቢኖር የፈረሱን ምግብ ለውሻ ባልሰጠነው ። ሀገር ይኑረን ከፋፋዮችን በቃቹ እንበላቸው!!


ፍቅሬ ነኝ  

No comments:

Post a Comment