የፍኖተ ነጻነት ምክትል ዋና አዘጋጅ የሆኑት አቶ ብዙአየሁ ወንድሙ ለኢሳት እንደገለጡት በተለይ ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በሁዋላ በተደጋጋሚ ” በቅርብ ቀን ትገደላለህ ” አቶ መለስ ከመቀበሩ በፊት አንተ ትቀበራልህ የሚል የስልክ መልእክት ሲደርሳቸው መቆየቱን አውስተው፣ በዛሬው እለትም ተመሳሳይ መልእክቶች ሲደርሳቸው መዋሉን ተናግረዋል::
የአንድነት ፓርቲ የብሄራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ዘካርያስ የማነአብ እንደገለጡት ፓርቲው በልሳኑ ላይ የተጣለበትን እገዳ ለመቃወም ህዝቡ ወደ አደባባይ እንዲወጣ ጥሪ እስከማድረግ የሚደርስ እርምጃ ይወስዳሉ::
No comments:
Post a Comment