Wednesday, November 9, 2011

የቀድሞው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ፕሬዚዳንት የነበረው ያረጋል አይሸሹም ንብረት በወያኔ ፍርድ ቤት ታገደ። የግለሰቡ ሃብት ባለሥልጣናቱ የተዘፈቁበትን ሙስና መጠን አመልካች ነው ተባል

በያረጋል አይሸሹምና በህወሀት ባለስልጣናት መካከል በተነሳው የፖለቲካ ውዝግብ ምክንያት ቀደም ሲል ታማኝነቱንና ታዛዥነቱን ለማግኘት ሲባል በተከፈተለት የሙስና በር በራሱና በቤተሰብቹ ስም እስከዛሬ ያከማቸው ሃብትና ንብረት እንዳይንቀሳቀስ የወያኔ ፍርድ ቤት ማገዱን ዘጋቢያችን ከአዲስ አበባ በላከልን ሪፖርት ገለጸ።
ፍርድ ቤት ተብዬው የወያኔ የማጥቂያ መሳሪያ፤ በያረጋል አይሸሹም፤ በባለቤቱ በትግስት በቃልና፣ በልጆቹ ስም ተመዝግበው የሚገኙ ንብረቶችን ያገደው፤ በአሶሳ በ1200 ስኩየር መሬት ላይ የሰፈረ የግል መኖሪያ ቤትና ሌላ ተጨማሪ 1000 ካሬ ሜትር ቦታ፣ በአዲስ አበባ ከተማ በቦሌ አካባቢ የሚገኝ 500 ካሬ መሬት፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ የሚገኝ 4132 ካሬ ቦታ፣ በኦሮሚያ ክልል የሚገኝ 500 ስኩየር ሜትር ላይ የሰፈረ በአለአንድ ፎቅ ህንጻና አንድ ሌላ የኮንዶሚኒየም ቤት፣ ምግብ ቤት እንዲሁም በልጁ ስም የተመዘገበ 1490 ካሬ መሬት ቦታ እንደሆነ ታውቆአል።
ቀሪውን ዋና ምንጭ ከሆነው ከሚከትለው ድህረገፅ ያንብቡት:  http://www.ginbot7.org/amh_wp/?p=2257

No comments:

Post a Comment